Épisodes

  • ማሕደረ ዜና፣የሱዳን ዉድመትና የመከፋፈሏ ሥጋት
    Apr 21 2025
    ያለመግባባቱ ምክንያቶች ከሩቅ ያሉት በቅኝ ገዢነት ብዙ ጊዜ የሚወቀሱት አዉሮጶች፣ በአረብ ጠላትነት የምትወገዘዉ እስራኤል ወይም አሜሪካኖች አይደሉም።የሱዳንን ሕዝብ «ወንድም» የሚሉት፣ከአብዛኛዉን ሱዳናዊ ጋር ቋንቋ፣ ባሕል፣ ኃይማኖት የሚጋሩት አረቦች እንጂ።ሳዑዲ አረቢያ፣ ግብፅና የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች በጋራ መግለጫዉ ይዘት ላይ አልተስማሙም።
    Voir plus Voir moins
    12 min
  • ማሕደረ ዜና፣የሱዳን ዉድመትና የመከፋፈሏ ሥጋት
    Apr 21 2025
    የለንደኑ ጉባኤ የተደረገዉ ጄኔራል መሐመድ ሐምዳን ዳጋሎ ያደረጁት «የሱዳን የሰላምና የአንድነት» ወይም የሱዳን ትዩዩ መንግሥት መመሥረቱ ናይሮቢ ላይ በታወጀ ማግሥት፣አል ቡርሐን የሚመሩት መንግስት የተባበሩት አረብ ኤምሬቶችን በዘር ማጥፋት ወንጀል የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ፍርድ ቤት ላይ በከሰሰ ሳልስት ነበር።ሚዚያ 16።ጄኔራል መሐመድ ሐምዳን ዳጋሎ የሚመሯቸዉ ቡድናት በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የገንዘብ ድጋፍ፣በኬንያዉ ፕሬዝደንት ዊሊያም ሩቶ አስተናጋጅነት የትይዩ መንግስት መመሥረታቸዉን ግብፅና ሳዑዲ አረቢያ አዉግዘዉታል
    Voir plus Voir moins
    12 min
  • ማሕደረ ዜና፣ የኢራን-አሜሪካ ድርድር ጠብ-ግጭቱን ያበርድ ይሆን?
    Apr 14 2025
    የሙጃህዲያን ኢ-ኻሊቅ (MEK)ና የቡድኑ ምክር ቤት መሪዎች ኢራን በ1967 ከአሜሪካ ባገኘችዉ ድጋፍ የጀመረችዉን የኑክሌር መርሐ ግብርን ወደ ኑክሌር ቦምብ መስሪያነት ለመቀየር ናታንዝና አራክ ዉስጥ በድብቅ እያብላላች መሆኑን ለዓለም አረዱ።ወይም አበሰሩ።ነሐሴ 2003።ዋሽግተን።ሲሞን ሔርሽና ኮኒ ብሩክ የተባሉት መርማሪ ጋዜጠኞች እንደፀፋት የሙጃህዲያን ኢ-ኻሊቅ መሪዎች የቴሕራኖችን ሚስጥር እንዲያጋልጡ የገፋፏችዉ መረጃዉንም የሰጧቸዉ የእስራኤል ባለሥልጣናት ናቸዉ።
    Voir plus Voir moins
    15 min
  • ማሕደረ ዜና፣ የአሜሪካና የኢራን ፍጥጫ-የመካከለኛዉ ምሥራቅ ምሥቅልቅል ሌላ ገፅታ
    Apr 7 2025
    የቴሕራን የፖለቲካና የጦር ሹማምንት ደግሞ ለፕሬዝደንት ትራምፕ ዛቻ አፀፋ ዛቻ እየሰነዘሩ ነዉ።የአያቶላሕ ዓሊ ኻማኒይ የቅርብ አማካሪ አሊ ላርጃኒ ባለፈዉ ሳምንት እንዳሉት ኢራን የኑክሌር ቦምብ መታጠቅ አትፈልግም።የአሜሪካኖች ዛቻ ከበረታ ግን ቀጠሉ የቀድሞዉ የኢራን የኑክሌር ጉዳይ ተደራዳሪ «ሌላ ምርጫ የለንም---መታጠቅ እንጂ።»
    Voir plus Voir moins
    14 min
  • ማሕደረ ዜና፣ የኢትዮጵያ ፈርጀ ብዙ ቀዉስ
    Mar 31 2025
    የብርቱካን ተመስገን ትረካ እዉነት-ሐሰትነት ለብዙዎች በጣሙን እሁለት ለተገመሱት ለማሕበራዊ መገናኛ ዘዴ አስተያየት ሰጪ-ተከታታዮች ማከራከሩን እንደቀጠለ ነበር።ግን እንዲያዉ ለመጠየቅ ያሕል 120 ሚሊዮን የሚሆነዉ የኢትዮጵያ ሕዝብ ሐቁን የሚያወጣ አንድ መርማሪ ፖሊስ፣ አንድ መርማሪ የሕግ ባለሙያ፣ አንድ መርማሪ ጋዜጠኛ፣ አንድ የምክር ቤት አጣሪ ኮሚቴ እንዴት አጣ?
    Voir plus Voir moins
    15 min
  • ማሕደረ ዜና፣ ሱዳኖች አንድም ሁለትም ሆነዉ ከግጭት-ጦርነት ያልተዩ ሐገራት
    Mar 24 2025
    የማቻር ደጋፊ የሚባሉት የኑዌር ጉሳ ሚሊሻዎች ኢትዮጵያን በሚያዋስነዉ ድንበር አካባቢ ከሠፈረዉ ከፕሬዝደንት ሳልቫኪር መንግስት ጦር ጋር መዋጋት ከጀመሩ ሳምንት አልፈዋል።የጁባዎች ጠብ የናረዉ ጁባዎች ከጋራንግ ሞት በኋላ እንዳደረጉት ሁሉ ከአል በሽር መወገድ በኋላ ዋና እና ምክትል ሆነዉ የካርቱም ሪፐብሊካን ቤተ መንግስትን የተቆጣጠሩት የሱዳን ጄኔራሎች የገጠሙት ጠብ በጦር ሜዳዉም በፖለቲካዉም መስክ ወደ አዲስ ምዕራፍ በተሸጋገረበት ወቅት መሆኑ ነዉ።የፈጥኖ ደራሹ ጦር ከደቡብ ሱዳን ቡድናት ካንደኛዉ ጋር ያለዉን ትብብር ከማጠናከርም አልፎ የትይይዩ መንግስት--- ዳርፉር ግዛት ሊመሰርት ይችላል የሚለዉ ግምትም እያየለ ነዉ
    Voir plus Voir moins
    13 min
  • “መፈንቅለ-መንግሥት” ወይስ “ሕግ ማስከበር” የትግራይ ቅርቃር
    Mar 17 2025
    የህወሓት አመራሮች ልዩነት ሲበረታ በደም አፋሳሽ ጦርነት ውስጥ ያለፈው የትግራይ ክልል ነዋሪ “ነገስ ምን ይፈጠራል?” በሚል “እየተሳቀቀ እንዲኖር” ተገዷል። ነዋሪዎች እንደሚሉት ጦርነት ይቀሰቀሳል በሚል ሥጋት “ሰዉ በጣም ተረባብሿል”፤ በኅብረተሰቡ ዘንድ “መከፋፈል” ተፈጥሯል። ነጋዴዎች የዋጋ ጭማሪ በማድረጋቸው “የኑሮ ውድነቱ እያሻቀበ” ነው።
    Voir plus Voir moins
    11 min
  • ደቡብ ሱዳን ወደ የርስ በርስ ጦርነት ዳግም እየተንሸራተተች ይሆን?
    Mar 10 2025
    ከኢትዮጵያ ድንበር 30 ኪሎ ሜትር በምትርቀው ናስር ከተማ በደቡብ ሱዳን ጦር ሠፈር ላይ የተፈጸመ ጥቃት ጁባን ፖለቲካዊ ውጥረት ውስጥ ከቷታል። በናስር በሚገኝ የደቡብ ሱዳን የጦር ሠፈር ላይ ባለፈው ሣምንት ጥቃት የፈጸመው ዋይት አርሚ ተብሎ የሚጠራ የኑዌር ጎሳ ታጣቂ ቡድን ነው። ፕሬዝደንት ሳልቫ ኪር ምክትላቸው ሪየክ ማቻርን ሳያማክሩ የወሰዷቸው ርምጃዎችም ቅሬታ ፈጥረዋል። ሁለቱ የተፈራረሙት የሰላም ሥምምነት ፈርሶ ደቡብ ሱዳን ወደ የርስ በርስ ጦርነት እንዳትገባ ሥጋት አለ።
    Voir plus Voir moins
    13 min